ጎንደር —
በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል የድንበር ማካለል ሥራ እንደሌለ የሰሜን ጎንደር ዞን አስተዳዳሪ ለቪኦኤ ገለፁ፡፡
“ከአሉባልታና ከወሬ ያለፈ ነገር የለም” ብለዋል አስተዳዳሪው፡፡
አንዳንድ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ደግሞ በውጭ መገናኝ ብዙኃንና በማኅበራዊ መገናኛዎች ድንበር የማካለል እንቅስቅስሴ እንዳለ ይናገራሉ።
ከድንበር አከባቢ ተፈናቅለዋል ወይም ተሰድደዋል የሚሏቸውንም በዋቢነት ያቀርባሉ።
መለስካቸው አምሀ በአካባቢው ተገኝቶ ነዋሪዎችንና ባለሥልጣናትን አነጋግሯል፡፡
የዘገባውን የመጀመሪያ ክፍል ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡