በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በዮናታን ላይ የተላለፈው ውሳኔ የመናገር ነፃነትን የሚፃረርና “አሳፋሪ” ነው ሲል አምነስቲ ገለፀ


በእስር ላይ የሚገኘው የቀድሞው የሰማያዊው ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ላይ ሽብርተኝነትን በማበረታታት በሚል በቀረበበት ክስ የተላለፈው የጥፋተኝነት ውሳኔ ሐሳብን የመግለፅና እና በፌስቡክ ፁሑፎችን የማውጣት መብት የሚፃረር “አሳፋሪ” ውሳኔ ነው ሲል ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ገለፀ።

በእስር ላይ የሚገኘው የቀድሞው የሰማያዊው ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ላይ ሽብርተኝነትን በማበረታታት በሚል በቀረበበት ክስ የተላለፈው የጥፋተኝነት ውሳኔ ሐሳብን የመግለፅ እና በፌስቡክ ፁሑፎችን የማውጣት መብት የሚፃረር “አሳፋሪ”ውሳኔ ነው ሲል ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ገለፀ።

የአምነስቲ የአፍሪካ ቀንድ ተመራማሪ አቶ ፍሰሃ ተክሌ “ይህ የሚያሳየው መንግሥትን የሚቃወሙ ወይም ከመንግሥት የተለየ ሐሳብ የሚያራምዱ ሰዎች በኢትዮጵያ ተቀባይነት እንደሌላቸውና ሕጉንም በመጠቀም ወንጀለኛ እንደሚባሉ የሚያሳይ ነው”ብለውታል።

እንዲህ ያለ ውሳኔ አዲስ አለመሆኑን የተናገሩት ተመራማሪው “ነገር ግን ዮናታን የጥፋተኝነት ውሳኔው የተላለፈበት ፌስቡክ ላይ በሚያወጣቸው አቋሞቹ ምክንያት በመሆኑ መንግሥት በእንደዚህ ዓይነት ተቃውሞዎችና ሂሶች ያለውን አቋም የሚያሳይ ጉዳይ ነው” ብለዋል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

በዮናታን ላይ የተላለፈው ውሳኔ የመናገር ነፃነትን የሚፃረርና “አሳፋሪ” ነው ሲል አምነስቲ ገለፀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:33 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG