በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑካን ቡድን የመጨረሻ ሪፖርቱን ይፋ አደረገ።


የመጨረሻ ሪፖርቱን በአዲስ አበባ ይፋ እንዳያደርግ የኢትዮጵያ መንግስት የወሰደውን የማገድ እርምጃ «ኢ-ዲሞክራሲያዊ ነው፤» ሲል የነቀፈው የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑካን ቡድን፤ በምርጫ ትዝብቱ ተመለከትኩ ያላቸውን ግድፈቶች በዛሬው ዕለት በብራስልስ ባካሄደው ጋዜጣዊ መግለጫው ዘርዝሯል።

ከብሄራዊው የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የቀረበለትን ግብዣ ተከትሎ ባለፈው ግንቦት በኢትዮጵያ የተካሄደውን ብሄራዊ ምርጫ የታዘበው የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ የመጨረሻ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል።

የድርጅቱ ዋና መቀመጫ በሚገኝባት የቤልጂጓ መዲና ብራስልስ ይፋ ያደረገውን ይህንን ሪፖርት ተንተርሶ የተጠናቀረውን ዘገባ አቢይ ርዕሳችን ይመለከተዋል። ለዝርዝሩ ዘገባውን ያድምጡ።

ተመሳሳይ ርእስ

XS
SM
MD
LG