በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የዩናይትድ ስቴትስ የምክር ቤቶች ምርጫና ዓለም አቀፍ አንድምታው


በዚህ በዩናይትድ ስቴትስ ማክሰኞ ጥቅምት 23 የሚካሄዱት Midterm Elections በመባል የሚታወቁት የአጋማሽ ጊዜ ምርጫዎች፤ በአሁኑ ወቅት አብላጫውን የሁለቱን ምክር ቤቶች የኅግ አውጪውንና የእንደራሴዎች ምክር ቤቶች፤ መቀመጫዎች ለያዘው የፕሬዝዳንት ኦባማ የዲሞክራቶች ፓርቲ ፈተና ይደቅናል፤ ተብሎ ተገምቷል።

የሪፐብሊካኑ ፓርቲ የብልጫውን ድምፅ ያገኝ ይሆናል፤ የሚል ሠፊ ግምት በተያዘባቸው በእነኚህ የአጋማሽ ጊዜ ምርጫዎች፤ በርካታ መቀመጫዎችን ያጡ ይሆናል የተባሉት ዲሞክራቶች፥ ከተቀናቃኛቸው በሚገጥማቸው ፈተና፥ ከዲሞክራቱ ፓርቲ የሆኑት ፕሬዝዳንት ኦባማ በቀጣዩ የሁለት ዓመታት የሥልጣን ዘመናቸው ለማሳካት ያቀዷቸው ውጥኖች «ይደናቀፋሉ፤» የሚል ግምት አሳድሯል።

እንደ ቅድመ ምርጫ ትንበያዎቹ ሪፐብሊካን የሁለቱንም ምክር ቤቶች አብላጫ መቀመጫዎች ከያዙ፥ የተባሉት ለውጦች፥ በአገር ውስጥ ጉዳዮች ብቻ ሳይወሰኑ፥ የዩናይትድ ስቴትስን የውጭ ፖሊሲ ጨምሮ፥ አሜሪካ በዓለም አቀፍ ደረጃ በምታጨወታቸው «ዋና ዋና የሚሰኙ ሚናዎቿም ይንፀባረቃሉ፤» እየተባለ ነው።

በርዕሱ ዙሪያ ትንታኔ የሚሰጡን የፖለቲካ ሳይንቲስት ጋብዘናል። ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም በካሊፎርኒያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህርና የህግ ባለ ሞያ ናቸው።

XS
SM
MD
LG